የሥራ ማስታወቂያ 01/04/17

የቅድስት ማርያም ዩኒቨርሲቲ ከዚህ በታች በተገለፀው ክፍት የሥራ መደብ ብቁ አመልካቾችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል፡፡

የስራ መደብ : ኦዲዮ ቪዥዋል ካሜራ ሰራተኛ ተፈላጊ የት/ት ደረጃ በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ/አይ ሲ ቲ በደረጃ III ወይም IV የተመረቀ/ች፤ በቪዲዮግራፊና ፎቶግራፊ የሰለጠነ(ች) እና የስራ ልምድ ማቅረብ የሚችል/ምትችል ብዛት (1)

ማሳሰቢያ፡- ለሥራ መደቡ የተጠየቀውን መስፈርት የምታሟሉ አመልካቾች የትምህርት ማስረጃችሁን ዋናውንና ፎቶ ኮፒውን በመያዝ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 4 ተከታታይ የሥራ ቀናት ውስጥ በዩኒቨርስቲው የሰው ኃብት አስተዳደር ቢሮ በመቅረብ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡

አድራሻ፡- ሜክሲኮ ከፌደራል ፖሊስ ዋና መ/ቤት ወደ አፍሪካ ሕብረት በሚወስደው መንገድ ከሚገኘው የኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት በስተቀኝ በኩል ወደ ውስጥ 200 ሜትር ገባ ብሎ በሚገኘው ዋናው መ/ቤት፡፡
ለበለጠ መረጃ 0115503193

ቅድስት ማርያም ዩኒቨርስቲ
የሰው ሀብት አስተዳደር ቢሮ